ፓርላማውና የአብይ አህመድ ስላቅ!!!

Jawar mohamed
June 15 2022

በጋዜጣዉ voice|ET News by Dawit Atreso

የአብይን ንግግር ታግሶ መስማት በጣም አታካች ነው።ከተለመደው ውጪ ምን ሊያስተላልፍ ይችላል ማለት ተገቢ ጥያቄ ቢሆንም ነገር ግን ምንም የተለየ ነገር አልተናገረም። በ 2013 ከተከፈተው የትግራይ ህዝብን ማውደም ዘመቻ እና ኢትዮጵያ የምትባል ሃገርን በተጠና መንገድ ለማፍረስ የኦሮሞው መንግስት ከጀምረ ሰነባብቷል። በተለይም የኢትዮጵያን ሰሜንን ክፍል 30 ዓመት ውደ ኋላ በመመልስ ለወደፊቷ ኦሮሚያ ሌት ተቀን በመስራት ላይ ይገኛል። ለዚህም ይመስላል በተቃዋሚ ተርታ የምናውቃቸው አንድ አንድ ፖለቲከኞች አብይን በይፋ መደገፍ የጀመሩት ።

ከምንጫችን እንደተረዳነው በዚህ አራት አመት ውስጥ ብቻ ከ 1400 በላይ ምልምሎችን ከኦሮሚያ ክልል በመምረጥ የደህንነት ስልጠና እንዲያገኙ አድርገዋል። ይገርማል!! ጠቅላይ ሚንስትሩ በፓርላማው ከተናገሩት መካከል በአማራ ክልል እና በትግራይ ክልሎች መካከል ስለሚደረገው ድርድር እና የወልቃይት ውዝግብ ጥያቄ በአቶ ደሳለኝ ጫኔ ሲቀረበላቸው፤ የመለሱት የነበረው የእሳቸው ሃላፊነት እንዳልሆነ በመግለፅ አቶ ደመቀ መኮንን እንዳሉበት ተናግረዋል ።

ጠቅላይ ሚንስትሩ በተጨማሪም የአዲስ አበባ ህዝብ ላይ የዘረኝነት ቦንብ ጥለው ውርደዋል። ከተናገሩት ውስጥ በሰሞኑ በይፋ ለወጣው መረጃ ማለትም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ባሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የኦሮሚያ ብሄራዊ መዝሙር በክፍለ ከተማው አስተዳደር በሚደገፍ መልኩ ተማሪዎች እንዲዘምሩ መደረጋቸውን፤ የውጪ ሃገራት ትምህርት ቤቶች በከተማዋ ብሄራዊ መዝሙራችውን እንደሚያዘምሩ ገለፀው የኦሮምኛ ቋንቋ በህገወጥ መንገድም ቢሆን ቢዘመር ግድ እንደማይሰጣችው ተናግረዋል።

ስለምትከታተሉን እናመሰግናለን!!!!!